ክሪስቶ ማግሊያሪስ ቤት።
ክሪስቶ ማግሊያሪስ ቤት።
ሰሜን ሆቴል ፊት ለፊት አዲስ አበባ
ክሪስቶ ማግሊያሪስ ከ1910 እስከ 1913 እኤአ ባለው ጊዜ ውስጥ ቤቱን የገነባው ከንጉሣዊ ቤተሰብ በውድ ካባ ልዋጭ ባገኘው መሬት ነበር። በአድዋ መንገድ በሚገኘው የግሪክ ቤተክርስቲያን ሰርጋቸውን የፈጸሙት ክሪስቶ እና ባለቤታቸው የመጀመሪያዎቹ ጥንዶች ነበሩ ።
የግሪክ ሠዓሊዎች ክፍሎቹን አስጌጠው ነበር፣ አሁን ግን ያ ጌጥ በውስጠኛው ክፍል አይታይም። የውስጠኛው የእንጨት ደረጃ በግሪክ ደሴት ባህላዊ ኪነህንጻ የተቃኘ ነው።
በኋላ ላይ በሕንድ ዘይቤ ፋኖስ የተጨመረ ሲሆን የሙሶሎኒ የራስ ቁርን ለማስመሰል ነው እየተባለም ይወራል።
ክሪስቶ በትውልድ ቦታው ጦርነትን ሸሽቶ አዲስ ከተማ ከተቀመጠ በኋላ የኖራን ምርትን ማምረት ጀመረ። ቤቱን ለመሥራት ተመሳሳይ ኖራ ጥቅም ላይ ውሏል. በ 1936 እና 1941 እኤአ መካከል, ቤቱ የጣሊያን ጄኔራል መኖሪያ ሆነ። የዩኤስ መኮንኖች በቬትናም ጦርነት ግዜ ለሶስት አመታት ኖረዋል።
የመጀመርያው ምስል ከ1960 እስከ 62 ባለው የተነሳ ሲሆን ሁለተኛው በ2014 የተነሳ ነው።
ምንጭ Old Tracks in the New Flower. Batistoni & Chiari. PP 93-94, HETTCL ፌቡ ገጽ፣ ዳዊት በንቲ።
@ethiopianarchitectureandurbanism






Reviews
There are no reviews yet.